አክሱም, የካቲት 19 ቀን 2002 (አክሱም) - የብሄረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ብአዴን/ የትጥቅ ትግል በጀመረበት በትግራይ ማእከላዊ ዞን በቆላ ተንቤን ወረዳ በሁለት ሚሊዮን ብር ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እያስገነባ መሆኑን የወረዳው ትምህርት ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡የጽህፈቱ ቤት ኃላፊ አቶ በሪሁ ኪዳነ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለፁት ንቅናቄው በወረዳው ጉያ ቀበሌ በመገንባት ላይ ያለው ትምህርት ቤት በአሁኑ ወቅት 80 ከመቶ ተጠናቋል፡፡
ትምህርት ቤቱ የመማሪያ ክፍሎች፣ ቤተ መፃህፍትና ሌሎች አገልግሎት መስጫ ክፍሎች እንዳሉት ገልጠው በሚቀጥሉት ሁለት ወራት ተጠናቆ አገልግሎት ሲጀምር በሁለት ፈረቃ አንድ ሺህ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተናገድ እንደሚችል አስታውቀዋል፡፡
በሌላ በኩል የወረዳው መስተዳድር ለብአዴን ያለውን ፍቅርና አክብሮት ለመግለጽ ከግማሽ ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ ተገንብቶ ሰሞኑን አገልግሎት መስጠት የጀመረውን ትምህርት ቤት የብአዴን አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተብሎ እንዲጠራ መሰየሙን ገልፀዋል፡፡
አገልግሎት የጀመረው አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 300 ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር የሚችል ነው፡፡
ሪፖ፡ 5፡05 ኤ1፡5፡30-5፡45 6፣00---END---