በደደቢት የተለኮሰው ችቦ ወደመላው ትግራይ ጉዞ ጀመረ
ሽሬ እንዳስላሴ, የካቲት 2 ቀን 2002 (ሽሬ እንዳስላሴ) የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ /ህወሓት/ 35 ዓመት የምስረታ በዓል ምክንያት በማድረግ የትጥቅ ትግሉ የተጀመረበት ደደቢት በረሃ

ትናንት የተለኮሰው ችቦ ወደመላው ትግራይ ክልል የሚያደርገውን ጉዞ ጀመረ ።

የትጥቅ ትግሉ በተጀመረበት ደደቢት ተገኝተው ችቦውን የለኮሱት የክልሉ ሴቶች ጉዳይ ቢሮ ሓላፊ ወይዘሮ ሮማን ገብረ ስላሴና የትጥቅ

ትግሉ ሲጀመር በአካባቢው የነበሩ የ68 ዓመቱ አዛውንት አቶ ካህሳይ ገብረ መድህን ናቸው።

የደደቢት ችቦ በሚል ስያሜ ተለኩሶ ጉዞውን የጀመረው ችቦ ዓላማ ሰላም፣ ዴሞክራሲ፣ ፍትህና ልማት በሀገሪቱ እንዲሰፍን አኩሪ መስዋእትነት የከፈሉትን ሰማእታትና በህይወት ያሉትን ታጋዮች ፅናት አዲሱ ትውልድ ተገንዝቦ የኢትዮጰያን ህዳሴ እውን እንዲያደርግ መልእክት ለማስተላለፍ እንደሆነ የጉዞው አስተባባሪ አቶ ሰለሞን አባዲ ገልፀዋል።

ችቦው መላውን ትግራይ ካዳረሰ በኋላ የካቲት 10 በመቀሌ ከተማ በመድረስ በሰማእታት ሃውልት በክብር እንደሚቀመጥ ተናግረዋል።

በደደቢት በተከናወነው የችቦ መለኮስ ስነ ስርዓት ላይ የተገኙት የትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ዋና አስተዳሪ አቶ ሚካኤለ አብርሃ

በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት ለሰላም፣ ለዴሞክራሲና ለልማት ክቡር ህይወታቸውን የከፈሉት ሰማእታት አደራ እንዲሳካ

ድህነትን የማስወገድ የተጀመረው እንቅስቃሴ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስታውቀዋል፡፡

ሪፖ፡ ያ፡ ኤ1፡3፡10-3፡20

---END---

Headlines
በደደቢት የተለኮሰው ችቦ ወደመላው ትግራይ ጉዞ ጀመረ
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ከ210ሺ600 በላይ ህዝብ በመራጭነት ተመዘገበ
በ274 ሚሊዮን ብር የመንገድ ግንባታ እየተካሄደ ነው
በሰሜን ጎንደር የሰፈራ ፕሮግራም ውጤታማ መሆኑ ተገለጸ
(c) The Ethiopian News Agency