አዲስ አበባ, ጥቅምት 15 ቀን 2000 (አዲስ አበባ) - የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ በድጋሚ መመረጣቸውን በማስመልከት የቼክ ሪፑብሊክ ፕሬዚዳንት ቫክላቭ ክላውስ የደስታ መግለጫ አስተላለፉ።የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ዓርብ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው ፕሬዚዳንት ክላውስ በመልእክታቸው በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት ይበልጥ እየተጠናከረ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በቅርቡ የቼክ ሪፑብሊክ ተቀዳሚ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ዩሪ ኩኔክ በኢትዮጵያ ጉብኝት ማድረጋቸው ለግንኙነቱ መጠናከር አይነተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አመልክተዋል።
የፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ በድጋሚ መመረጥ ግንኙነቱ በይበልጥ እንዲጠናከር አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ዕምነታቸው መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል ሲል መግለጫው አስታውቋል።
ሪ1፡15 ያ1፡22 የ1፡45
---END---