አርባ ምንጭ, ጥቅምት 15 ቀን 2000 (አርባምንጭ) - የአርባ ምንጭ ዩኒቪርሲቲ በዚህ አመት ሁለት አዲስ ፋኩሊቲዎች መክፈቱን አሰታወቀ፡፡የዩኒቪርሲቲው ፕሬዜዳንት ዶክተር ታረቀኝ ታደሰ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጡት ዩኒቪርሲቲው ዘንድሮ የከፈታቸው ፋኩሊቲዎች የእርሻና የጤና ሳይንስ ናቸው፡፡
አዲስ የተደራጁት እነዚህ ፋኩሊቲዎች 800 ተማሪዎችን ተቀብለው በተለያየ ፕሮግራም ስልጠና መጀመራቸውንም ተናግረዋል፡፡
ፋኩሊቲዎቹ የተከፈቱት ቀደም ሲል ተቀርጾ ስራ ላይ በዋለው የዩኒቪርሲቲው የአምስት አመት ስትራቴጂክ እቅድ መሰረት እንደሆነም አብራርተዋል፡፡
ወደፊት ሌሎች ፋኩሊቲዎች እንደሚከፈቱ አመልክተው፣ ስትራቴጂክ እቅዱ ተግባራዊ ሲሆን ዩኒቪርሲቲው ዘጠኝ ፋኩሊቲዎች እንደሚኖሩትና የተማሪ ቅበላ አቅሙም 10 ሺህ እንደሚደርስ ፕሬዜዳንቱ ጠቁመዋል፡፡
ሰ/9.55 ያለ/ 10.55
---END---