አዲስ አበባ, ጥቅምት 15 ቀን 2000 (መቀሌ) - ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የሶማሊያን የሽግግር መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓሊ ሞሐመድ ጌዲን ዛሬ በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ፡፡ሁለቱ ጠቅላይ ሚኒስትሮች በውይይታቸው ወቅት በአፍሪካ ቀንድ በተለይ በሶማሊያ ሰላምና መረጋጋት ጉዳይ ላይ መወያየታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ጌዲ ከውይይቱ በኋላ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ጌዲ እንዳሉት በአሁኑ ወቅት በሞቃዲሾ ከተማና በመላዋ ሶማሊያ ሰላምና መረጋጋትን በሚገባ ለማረጋገጥ የሽግግር መንግሥቱ ጥረት እያደረገ ነው፡፡
የሽግግር መንግሥቱ ከጎረቤት አገራት በተለይም ከኢትዮጵያ ጋር ከመቼውም ጊዜ በተሻለ የትብብርና የመተጋገዝ መንፈስ ሶማሊያን ለማረጋጋት እየሠራ እንደሚገኝም አስታውቀዋል፡፡
ሪ9፡55 የ10፡03 ጥ መ
---END---