የመድሀኒት አስተዳዳርና ቁጥጥር ባለስልጣን ከአንድ የአሜሪካ ድርጅት ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ
አዲስ አበባ, ጥቅምት 15 ቀን 2000 (አዲስ አበባ) - የኢትዮጵያ መድሀኒት አስተዳዳርና ቁጥጥር ባለስልጣን ማኔጅመንት ሳይንስ ፎር ሄልዝ አር .ፒ.ኤም ፕላስ ከተባለ የአሜሪካ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የአምስት ዓመት የውል ስምምነት ተፈራረመ፡፡

በቅርቡ አዲስ አበባ ውስጥ የተካሄደውን ይህንኑ ስምምነት የፈረሙት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀይለስላሴ ቢሆንና የማኔጅመንት ሳይንስ ፎር ሄልዝ አር.ፒ.ኤም ፕላስ ቺፍ ኢን ፓርቲ ዶክተር ንጉሱ መኮንን ናቸው፡፡

የባለስልጣኑ መስሪያ ቤት ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጸው ስምምነቱ በመድሀኒት ዘርፍ መልካም አስተዳዳርን ለማስፈን፣ በአገሪቱ ጤና አገልግሎት ጥቅም ላይ የሚውሉ መድሀኒቶች ደህንነታቸው፣ ፈዋሽነታቸውንና ጥራታቸውን የማረጋጋጥ አቅም ለመገንባት ያስችላል፡፡

በተጨማሪም ስምምነቱ መድሀኒቶቹ በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲውሉ ለማድረግና የመድሀኒት አቅርቦት ማኔጅመንት ስርዓት ለማጠናከር እንዲሁም ጸረ ተህዋስያን መድሀኒቶች በተለያዩ ተህዋስያን በመለማማድ የፈዋሽነታቸውን አቅም እንዳያጡ ለመከላከልና ለመግታት የሚያስችሉ ስትራቴጂዎችን በመቅረጽ ስራ ላይ ለማዋል የሚረዳ ነው፡፡

ስምምነቱ መስሪያ ቤቱ በየዓመቱ የሚያቀርበውን እቅድ ተግባራዊ ለማድረግ በገንዘብ፣ በማቴሪያልና በቴክኒክ ረገድ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማግኘት ያስችለዋል፡፡

ሁለቱ መስሪያ ቤቶች በኢትዮጵያ የመድሀኒት አሰተዳደር ዘርፉን ለማጠናከር በቅንጅት ለመንቀሳቀስ የጋራ ሀላፊነት እንዳለባቸውም በውል ስምምነቱ ላይ ተቀምጧል፡፡

በተጨማሪም አካላቱ በተስማሙባቸው በስትራቴጂክ እቅድ የተቀመጡ ቁልፍ እቅዶችን ለማስፈጸምና ከተያዘው ከሚሌኒየሙ ጀምሮ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ከ17 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት መያዙን ባለስልጣኑ ገልጿል፡፡

የአምስት ዓመቱ እቅድ ከ2000 እስከ 2004 የሚከናወን ሲሆን በቀጣይነትም መስሪያ ቤቱ ዘርፉን ለማጠናከር ሌሎች በርካታ ፕሮጀክቶችን ነድፎ ከሌሎች መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር በጋራ አጠናክሮ እንደሚሰራ አስታውቋል፡፡

---END---

Headlines
ኤች አር 2003 ለኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ግንባታ የሚፈይደው አንዳችም ጠቀሜታ የለውም፤ በየደራጃውም ሊወገዝ ይገባል
ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የሶማሊያን የሽግግር መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓሊ መሐመድ ጌዲን አነጋገሩ
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሽብርተኝነት ለሰው ዘር ጠንቅ በመሆኑ ሊወገድ ይገባዋል ሲል ጥሪ አስተላለፈ
የቼክና የስሎቫክ ስድስት አገር አሳሾች በሕይወት መግኘት የሚያስደስት ነው
የቼክ ፕሬዚዳንት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ በድጋሚ መመረጣቸውን በማስመልከት የደስታ መግለጫ አስተላለፉ
ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሹመት ሰጡ
ሰዓሊዋ በኢትዮጵያ ያደረገችው ቆይታ እንዳስደሰታት ገለጸች
ዩኒቪርሲቲው አዲስ ፋኩሊቲዎች ከፈተ
በተለያዩ የዓለም አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ከ632 ነጥብ 6 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ወደአገር ቤት ልከዋል
በቤተሰብ የውሃ አሰተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ የሚነጋገር ዓለም አቀፍ ጉባኤ አዲስ አበባ ውስጥ ይካሄዳል
ድርጅቱ ሞዴሎችን በመምረጥ የፋሽን ትርዒት ሊያቀርብ ነው
የመድሀኒት አስተዳዳርና ቁጥጥር ባለስልጣን ከአንድ የአሜሪካ ድርጅት ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ
በኦሮሚያ ክልል ባለፈው የምርት ዘመን 152 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ተገንቷል፡፡
ኢትዮጵያውያን የራሳቸውን ባህልና ሐይማኖት በተከተለ ሁኔታ የሚሌኒየም በዓላቸውን እያከበሩ ናቸው የአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ
የፍትሕ ሚኒስቴር ተቋማዊ ለውጥ ማምጣቱን አስታወቀ
ቆነጃጅት የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጎበኙ
በልመና የተሠማሩ ሰዎች ወደመኖሪያቸው እንዲመለሱና እንዲቋቋሙ የበኩላቸውን ሚና እንደሚጫወቱ አርቲስቶች ገለጹ
ባለስልጣኑ የአደገኛ መድሀኒቶችና እጾች ህገወጥ ዝውውርና አጠቃቀምን ለመከላከል የአምስት ዓመት እቅድ አዘጋጀ
በትግራይ ክልል ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሰ 117ሺህ ሕጻናት ትምህርት ጀመሩ
በአርሲ ምርጥ ዘር በማባዛት ስራ የተሰማሩ አርሶ አደሮች እስከ 30 ሺህ ብር ድረስ ገቢ እያገኙ ነው
(c) The Ethiopian News Agency