አሰላ, ጥቅምት 15 ቀን 2000 (አሰላ) - በአርሲ ዞን በሒጦሳ ወረዳ በምርጥ ዘር ማባዛት ስራ የተሰማሩ አርሶ አደሮች እስከ 30 ሺህ ብር ገቢ በማግኘት ተጠቃሚ መሆናቸውን የወረዳው ግብርናና ገጠር ልማት ጽሕፈት ቤት ገለጠ፡፡የጽሕፈት ቤቱ ሃላፊ አቶ አበራ ለማ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጡት ባለፈው ዓመት በወረዳው ከ600 የሚበልጡ አርሶ አደሮች የስንዴ፣ባቄላና አተር ምርጥ ዘር በማባዛት ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡
በወረዳው ከሶስት ዓመት በፊት በአነስተኛ የእርሻ መሬት ላይ የተጀመረው ምርጥ ዘር የማባዛት ስራ የአርሶ አደሩን ገቢ እያሳገ በመምጣቱ የተሳታፊ አርሶ አደሮች ቁጥር መጨመሩን ገልጠው ምርጥ ዘሩን ከአርሶ አደሩ የምርጥ ዘር ድርጅት ከአካባቢው ዋጋ 30 ብር ጭማሪ በማድረግ እንደሚረከብ አስታውቀዋል፡፡
በያዝነው የምርት ዘመን 607 አርሶ አደሮች በ490 ሔክታር መሬት ላይ ምርጥ ዘር በማባዛት ላይ መሆናቸውን አስታውቀው ከ18 ሺህ ኩንታል የሚበልጥ ምርት ይሰበሰባል ተብሎ መገመቱንም ገልጠዋል፡፡
በልማቱ የተሳተፉ አርሶ አደሮች እንደየስራቸው ከአራት ሺህ እስከ 30 ሺህ ብር በነፍስ ወከፍ ገቢ ማግኘት እንደቻሉም አስታውቀዋል፡፡
ከተሳታፊዎቹ መካከልም አንዳንዶቹ በሰጡት አስተያየት ከምግብ ሰበል ጎን ለጎን ምርጥ ዘር በማባዛት ከፍተኛ ገቢ ማግኘት በመቻላቸው ከሳር ክዳን ቤት ወደ ቆርቆሮ መኖሪያ ቤት ከመሸጋገራቸውም ሌላ የንግድ ስራ የከፈቱም መኖራቸውን ገልጠዋል፡፡
ሪፖ 400 ኤዲ2 610
---END---