መቀሌ, ጥቅምት 15 ቀን 2000 (መቀሌ) - በትግራይ ክልል በያዝነው ዓመት ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሰ 117 ሺህ ሕጻናት ትምህርት መጀመራቸውን የክልሉ ትምሀርት ቢሮ አስታወቀ፡፡የቢሮው የፕላንና ስታትስቲክስ ቡድን መሪ አቶ ገብረ መድህን መሰል ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንዳስታወቁት ህጻናቱ ትምህርት የጀመሩት በአዲሱ ሚሌኒየም ሰባት ዓመት የሞላቸውን ሕጻናት ትምህርት ቤት ለማስገባት በተደረገው ጥረት ነው፡፡
ክንውኑ ካለፈው ዓመት በ7 ሺህ ብልጫ እንዳለውና ውጤቱም ሊገኝ የቻለው ወላጆች፣መምህራንና የወረዳ መስተዳድር አካላት ባደረጉት እንቅስቃሴ መሆኑን አመልክተዋል፡፡
ሕጻናቱን ለማስተናገድ ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎች ግንባታ፣የመምህራን ቅጥርና ተጓዳኝ ሥራዎች መከናወናቸውን ቡድን መሪው አስታውቀዋል፡፡
ክልሉ በዚህ ዓመት ወደ ትምህርት ቤት ለማስገባት ካቀደው 88 በመቶው ያህል ማሳካቱንም ገልጸዋል፡፡
ኤዲ1 6 00 ኤዲ2 635
---END---