በኦሮሚያ ክልል ባለፈው የምርት ዘመን 152 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ተገንቷል፡፡
አዲሰ አበባ, ጥቅምት 15 ቀን 2000 (አዲስ አበባ) - በኦሮሚያ ክልል ባለፈው የምርት ዘመን 6 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሔክታር መሬት መልማቱን የክልሉ ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ አስታወቀ፡፡

የቢሮው ኃላፊ አቶ ድሪባ ኩማ ለትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንዳስታወቁት በምርት ዘመኑ በክልሉ ምርትና ምርታማነትን ለማስመዝገብ በተደረገው ጥረት 152 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ተገንቷል፡፡

በክልሉ ምርትና ምርታማነትን ለማስመዝገብ የግብዓብት ዝግጅት መደረጉን አመልክተው በዚሁ ወቅት በመንግገስት 1ነጥብ 7 ሚሊዮን ኩንታል ከተለያዮ የግል አቅራቢ ድርጅቶች ደግሞ ከ200 ሺህ ያላነሰ ማዳበሪያ መሰራጨቱን አመልክተዋል፡፡

በዚሁ ወቅት መንግስት ለክልሉ አርሶ አደሮች 140ሺህ ኩንታል ምርጥ ዘር ማቅረቡንና አርሶ አደሩም በራሱ ማሳ ዘሮችን በማባዛት ለምርቱ እድገት አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልፀዋል፡፡

በዚሁ ወቅት የተለያዮ ሙያተኞችን በማሰልጠን ለስራ በማብቃትና ውጤታ እንዲሆኑ ተደርጓል ያሉት የቢሮው ሃላፊ ለ13 ሺህ 900 የልማት ሰራተኞችና የወረዳ ሙያተኞችን በአዲሱ የኤክስቴንሽንና ማሳ ዝግጅት ስራዎች ላይ ስልጠና ተሰጥተዋል ብለዋል፡፡

ከአራት ዓመት በፊት የክልሉ አጠቃላይ ምርት 48 ሚሊዮን ኩንታል እንደነበር አቶ ድሪባ አመልክተው ባለፉት አራት አመታት በተደረገው ርብርብም ወደ መርቱ ወደ 118 ሚሊዮን ኩንታል ከፍ ማለቱን አስረድተዋል፡፡

ከዚህ በፊት በኤክስቴንሽን ይሳተፍ የነበረው አርሶ አደር ከ300 ሺህ የማይበልጥ እንደነበርና በአሁኑ ወቅት ግን 3ነጥብ 6 ሚሊዮን አርሶዳር ተጠቃሚ አንደሆነ ገልፀዋል፡፡

አገሪቱ በግብርናው መስክ ላስመዘገበችው እድገት ክልሉ ከፍተኛ አስተዋጽኦኦ ያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ወደፊትም ይህንን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡

በክልሉ የታየውን የግብርና ምርት እድገት ቀጣይነት ለማስመዝገብ የተለያዮ አካላት ርብርብ የሚያስፈለግ ያሳሰቡት የቢሮው ሃላፊ የምርምር ተቋማት እያካሔዱ ያለውን የግብርና ምርምር ለአርሶ አደሩ በማድረስ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል፡፡

---END---

Headlines
ኤች አር 2003 ለኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ግንባታ የሚፈይደው አንዳችም ጠቀሜታ የለውም፤ በየደራጃውም ሊወገዝ ይገባል
ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የሶማሊያን የሽግግር መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓሊ መሐመድ ጌዲን አነጋገሩ
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሽብርተኝነት ለሰው ዘር ጠንቅ በመሆኑ ሊወገድ ይገባዋል ሲል ጥሪ አስተላለፈ
የቼክና የስሎቫክ ስድስት አገር አሳሾች በሕይወት መግኘት የሚያስደስት ነው
የቼክ ፕሬዚዳንት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ በድጋሚ መመረጣቸውን በማስመልከት የደስታ መግለጫ አስተላለፉ
ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሹመት ሰጡ
ሰዓሊዋ በኢትዮጵያ ያደረገችው ቆይታ እንዳስደሰታት ገለጸች
ዩኒቪርሲቲው አዲስ ፋኩሊቲዎች ከፈተ
በተለያዩ የዓለም አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ከ632 ነጥብ 6 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ወደአገር ቤት ልከዋል
በቤተሰብ የውሃ አሰተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ የሚነጋገር ዓለም አቀፍ ጉባኤ አዲስ አበባ ውስጥ ይካሄዳል
ድርጅቱ ሞዴሎችን በመምረጥ የፋሽን ትርዒት ሊያቀርብ ነው
የመድሀኒት አስተዳዳርና ቁጥጥር ባለስልጣን ከአንድ የአሜሪካ ድርጅት ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ
በኦሮሚያ ክልል ባለፈው የምርት ዘመን 152 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ተገንቷል፡፡
ኢትዮጵያውያን የራሳቸውን ባህልና ሐይማኖት በተከተለ ሁኔታ የሚሌኒየም በዓላቸውን እያከበሩ ናቸው የአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ
የፍትሕ ሚኒስቴር ተቋማዊ ለውጥ ማምጣቱን አስታወቀ
ቆነጃጅት የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጎበኙ
በልመና የተሠማሩ ሰዎች ወደመኖሪያቸው እንዲመለሱና እንዲቋቋሙ የበኩላቸውን ሚና እንደሚጫወቱ አርቲስቶች ገለጹ
ባለስልጣኑ የአደገኛ መድሀኒቶችና እጾች ህገወጥ ዝውውርና አጠቃቀምን ለመከላከል የአምስት ዓመት እቅድ አዘጋጀ
በትግራይ ክልል ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሰ 117ሺህ ሕጻናት ትምህርት ጀመሩ
በአርሲ ምርጥ ዘር በማባዛት ስራ የተሰማሩ አርሶ አደሮች እስከ 30 ሺህ ብር ድረስ ገቢ እያገኙ ነው
(c) The Ethiopian News Agency