ባለስልጣኑ የአደገኛ መድሀኒቶችና እጾች ህገወጥ ዝውውርና አጠቃቀምን ለመከላከል የአምስት ዓመት እቅድ አዘጋጀ
መድሃኒት አስተዳደር, ጥቅምት 15 ቀን 2000 (አዲስ አበባ) - የኢትዮጵያ መድሀኒት አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን የአደገኛ መድሀኒቶችና እጾች ህገወጥ ዝውውርና አጠቃቀምን ለመከላከልና ለመቆጣጣር የሚያስችል የአምስት ዓመት መሪ እቅድ ማዘጋጀቱን አስታወቀ፡፡

በኢትዩጵያ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ ብሄራዊ የመድሀኒት ፎርሙላሪ ማዘጋጀቱንም ገልጿል፡፡

በባለስልጣኑ የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያና የህዝብ ግንኙነት አገልግሎት ኋላፊ አቶ አማረ አሰፋ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት

ይኽው የአምስት አመት መሪ እቅድ በተያዘው ሚሌኒየም በተግባር ላይ ይውላል፡፡

መሪ እቅዱ የአደገኛ መድሀኒቶችና እጾች ህገወጥ ዝውውርና አጠቃቀም የሚገኝበትን ሁኔታ በጥልቀት በመገምገም ጠንካራና ደካማ ጎኖችን እንዲሁም ቁልፍ የሆኑ ችግሮችን በመለየት ራእይና ተልእኮ ያስቀመጠ ነው፡፡ በተጨማሪም ራእይና ተእልኮውን ዳር ለማድረስ የሚያስችሉ ቁልፍ ስትራቴጂዎችንም በዝርዝር ይዟል፡፡

ይህም እየተካሄደ ያለውን የአደገኛ መድሀኒቶች ህገወጥ ዝውውር የመከላከልና የመቆጣጣር ስራን ውጤታማ እንደሚያደርገው የህዝብ ግንኙነት አገልግሎት ኋላፊው ገልጸዋል፡፡

ኢትዮጵያ ይህን ዓለም ዓቀፍና አገር አቀፍ ችግር ለመከላከልና ለመቆጣጣር አለም አቀፍ የሆኑ ሶስት ስምምነቶችን ተቀብላላች፡፡

በዚህም ረገድ ፖሊሲዎችን በመቅረጽና ነባር ህጎችን በማሻሻል አስፈጻሚ አካላትን በየደረጃው በማደራጀት የህብረተሰቡን ግንዛቤ ለማሳደግ እየተደረገ ያለው ጥረት አሁንም ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል፡፡

ከዚሁ በተጨማሪ ባለስልጣኑ ያዘጋጀው ብሄራዊ የመድሀኒት ፎርሙላሪ በሁሉም ደረጃ ላሉ የጤና ድርጅቶችና የጤና ባለሙያዎች አገልግሎት ሊሰጥ የሚችል ነው፡፡

ቀደም ሲል ከወረዳ በላይ ላሉ የጤና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ፎርሙላሪ ያልነበራቸው መሆኑን ገልጸው አሁን የተዘጋጀው ብሄራዊ ፎርሙላሪ በአገሪቱ ላሉ የጤና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ባሉበት ደረጃ በፍጥነት መረጃ ለማግኘት የሚያስችላቸው እንደሆነም አቶ አማረ አመልክተዋል፡፡

ፎርሙላሪው ለማንኛውም ባለሙያ አጠቃላይ የመረጃ ምንጭ ሆኖ ከማገልገል በተጨማሪ ባለሙያው ስለማንኛውም መድሀኒት መረጃ ሲፈልግ የመድሀኒት ፎርሙላሪውን በማጣቀሻነት ሊጠቀም እንደሚችል ገልጸዋል፡፡

---END---

Headlines
ኤች አር 2003 ለኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ግንባታ የሚፈይደው አንዳችም ጠቀሜታ የለውም፤ በየደራጃውም ሊወገዝ ይገባል
ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የሶማሊያን የሽግግር መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓሊ መሐመድ ጌዲን አነጋገሩ
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሽብርተኝነት ለሰው ዘር ጠንቅ በመሆኑ ሊወገድ ይገባዋል ሲል ጥሪ አስተላለፈ
የቼክና የስሎቫክ ስድስት አገር አሳሾች በሕይወት መግኘት የሚያስደስት ነው
የቼክ ፕሬዚዳንት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ በድጋሚ መመረጣቸውን በማስመልከት የደስታ መግለጫ አስተላለፉ
ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሹመት ሰጡ
ሰዓሊዋ በኢትዮጵያ ያደረገችው ቆይታ እንዳስደሰታት ገለጸች
ዩኒቪርሲቲው አዲስ ፋኩሊቲዎች ከፈተ
በተለያዩ የዓለም አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ከ632 ነጥብ 6 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ወደአገር ቤት ልከዋል
በቤተሰብ የውሃ አሰተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ የሚነጋገር ዓለም አቀፍ ጉባኤ አዲስ አበባ ውስጥ ይካሄዳል
ድርጅቱ ሞዴሎችን በመምረጥ የፋሽን ትርዒት ሊያቀርብ ነው
የመድሀኒት አስተዳዳርና ቁጥጥር ባለስልጣን ከአንድ የአሜሪካ ድርጅት ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ
በኦሮሚያ ክልል ባለፈው የምርት ዘመን 152 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ተገንቷል፡፡
ኢትዮጵያውያን የራሳቸውን ባህልና ሐይማኖት በተከተለ ሁኔታ የሚሌኒየም በዓላቸውን እያከበሩ ናቸው የአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ
የፍትሕ ሚኒስቴር ተቋማዊ ለውጥ ማምጣቱን አስታወቀ
ቆነጃጅት የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጎበኙ
በልመና የተሠማሩ ሰዎች ወደመኖሪያቸው እንዲመለሱና እንዲቋቋሙ የበኩላቸውን ሚና እንደሚጫወቱ አርቲስቶች ገለጹ
ባለስልጣኑ የአደገኛ መድሀኒቶችና እጾች ህገወጥ ዝውውርና አጠቃቀምን ለመከላከል የአምስት ዓመት እቅድ አዘጋጀ
በትግራይ ክልል ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሰ 117ሺህ ሕጻናት ትምህርት ጀመሩ
በአርሲ ምርጥ ዘር በማባዛት ስራ የተሰማሩ አርሶ አደሮች እስከ 30 ሺህ ብር ድረስ ገቢ እያገኙ ነው
(c) The Ethiopian News Agency