አዲስ አበባ, ጥቅምት 13 ቀን 2000 (አዲስ አበባ) - የፖላንድ ፕሬዚዳንት ሌች ካችዚንስኪ ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ በድጋሚ በመመረጣቸው የተሰማቸውን ደስታ ገለጹ ፡፡የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንዳስታወቀው ፕሬዚዳንት ካችዚንስኪ በፖላንድ ሕዝብና መንግስት እንዲሁም በራሳቸው ስም በላኩት የደስታ መግለጫ ለፕሬዚዳንት ግርማ መልካም የሥራ ዘመን ተመኝተዋል ፡፡
ረጅም እድሜ ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገሮች ግንኙነትና ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ያላቸውን እምነት መግለፃቸውንም ሚኒስቴሩ አስታውቋል ፡፡
ሪ፡ 11፡10 ኤ2 11፡18 ጥጥ
---END---