አዲስ አበባ, ጥቅምት 13 ቀን 2000 (አዲስ አበባ) - ንግድና ኢንቨስትመንትን ወደ አፍሪካ ለመሳብ ብሎም የአህጉሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ በውስጥና በውጪ የሚያስተዋውቅ አዲስ ድረገጽ ተከፈተ፡፡"www.opportunitiesinxfrica.com ደብሊው ደብሊው ደብሊው ዶት ኦፖርቹኒቲስኢንአፍሪካ ዶት ኮም" የተባለውና በአፍሪካ ያለውን የንግድ ሁኔታ የሚያስተዋውቀው ይህ ድረ ገጽ በአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ድጋፍ የተዘጋጀ ነው፡፡
ዌብሳይቱ ዓለምአቀፍ ድርጅቶች በአህጉሪቱ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱና የንግድ ልውውጥ እንዲያደርጉ ብሎም ከአህጉሪቱ ኩባንያዎች ጋር ጠንካራ የንግድ ግኙነት እንዲመሠርቱ እድል እንደሚፈጥር ተገልጿል ፡፡
የአፍሪካ ኩባንያዎች ምርቶቻቸውን በዓለም ገበያ እንዲሸጡም ያስችላል ተብሏል፡፡
ድረ ገጹ የአፍሪካ መንግሥታት በአገሮቻቸው ያሉትን የኢንቨስትመንት አማራጮች ፣ በየአገራቱ የሚገኙ ኩባንያዎች ምርቶችና አድራሻ፣ የሚያስተዋውቁበትና የሚሸጡበት ገጾችን ያካተተ ነው፡፡
ድረ ገጹ የአፍሪካ አገራትና ኩባንያዎች የንግድ አማራጮቻቸውን ፣ ምርቶቻቸውንና አገልግሎቶቻቸውን ለመላው ዓለም እንዲያስተዋውቁ ተደርጎ መቀረጹን መቀመጫውን አየርላንድ ዱብሊን ያደረገው ኤች አር ኤ ኮሚዩኒኬሽንስ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አስታውቋል፡፡
ሪ-10፡05 ያ-10፡16 ኤ2 11፡39 ጥጥ
---END---