|
|
አዋሳ ግንቦት 10/2005 የኢትዮጵያን መልካም ገጽታ ለመገንባት የላቀ አስተዋጾኦ ያለውን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ስራን ለማፋጠን በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሀዋሳ ዩኒቨርሰቲ ተማሪዎች ገለጹ፡፡
|
|
|
|
አዳማ ግንቦት 10/2005 የግልና የመንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለአገሪቱ የህዳሴ ጉዞ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከት የሚችል ብቃቱ የተረጋገጠ የሰው ሃይል ማፍራት እንደሚጠበቅባቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥራት ማስጠበቅ ኤጄንሲ ገለፀ፡፡
|
|
|
|
አክሱም ግንቦት 10/2005 በትግራይ ማዕከላዊ ዞን በየአመቱ የሚካሄደው የገጠር ወረዳዎች የ4 አይነት የስፖርት ውድድር በውቅሮ ማራይ ከተማ ትናንት ተጀመረ ፡፡ የስፖርት ውድድር የታወቁና ሀገራችንን ሊያስጠሩ የሚችሉ ስፖርተኛች የሚመለመሉበት ነው ፡፡
|
|
|
|
አዋሳ ግንቦት 10/2005 በኦሮሚያ ክልል ከ1 ጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በበጀት ዓመቱ የተጀመሩ 259 የጤና ተቋማት ግንባታ በመፋጠን ላይ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡
|
|
|
|
አሰላ ግንቦት 10/2005 በአርሲ ዞን የሥነ ተዋልዶና የቤተሰብ ምጣኔ አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግ በተካሄደው እንቅስቃሴ ከ300ሺ በላይ የሚሆኑ ሴቶች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆናቸውን የዞኑ ጤና ጥበቃ መምሪያ አስታወቀ፡፡
|
|
|
|
ነገሌ ግንቦት 10/2005 በአርብቶ አደሩ አካባቢ የበልጉን ዝናብ ተከትሎ በእንስሳት ጤና ላይ ችግር እንዳይከሰት ከ621 ሺ ለሚበልጥ የቤት እንስሳት ክትባት መሰጠቱን የጉጂ ዞን እንስሳት ሀብት ገበያ ልማትና ጤና ኤጀንሲ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡
|
|
|
|
አሶሳ ግንቦት 10/2005 በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከግልገል በለስ ወደ አሶሳ የትራንስፖርት አገልግሎት እጥረት በመከሰቱ መቸገራቸውን ተገልጋዮች አመለከቱ፡፡
|
|
|
|
ማይጨው ግንቦት 10/2005 የመቀሌ ዩኒቨርስቲ ሕግና ፍትህ አተገባበር ስርዓት ለማሻሻል በፍትህ አካላት የሚሰጠውን የአቅም ግንባታ ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ፡፡
|
|
|
|
አዲሰ አበባ ግንቦት 10/2005 በሽመና ሥራ ዘርፍ የተሰማሩ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የሚያጋጥማቸውን የግብዓት ችግር ለመፍታት የሚያስችል ውይይት መደረጉን የፌዴራል የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡
|
|
|
|
አዲስ አበባ ግንቦት 10/2005 በትግራይ ክልል ከ534 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የማይፀምሪ - ዲማ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ተጠናቆ ተመረቀ፡፡
|
|
| |